የወታደሮቹና የቁምጣ ለባሾቹ ዕኩይ ድርጊት ሲፍረጠረጥ (በግልጥ አቀራረብ): የጓደኛሞቹ ወግ ክፍል - 1 (Afrikaans Edition)

★★★★★ 4.5 34 reviews

$13.17
Price when purchased online
Free shipping Free 30-day returns

Sold and shipped by fondationcepeo.ca
We aim to show you accurate product information. Manufacturers, suppliers and others provide what you see here.
$13.17
Price when purchased online
Free shipping Free 30-day returns

How do you want your item?
You get 30 days free! Choose a plan at checkout.
Shipping
Arrives Jul 20
Free
Pickup
Check nearby
Delivery
Not available

Sold and shipped by fondationcepeo.ca
Free 30-day returns Details

Product details

Management number 236963784 Release Date 2026/07/10 List Price $5.27 Model Number 236963784
Category

መንግሥት ሥልጣኑንና የራሱን ርእዮተ ዓለም በግዴታ በህዝቡ ላይ ለመጫን ብሎ ህገ ወጡን አካሄድ ህጋዊ በማድረግ የሰው ዕልቂት እንዲፈጠር በማድረግ የሚጓዘው ለምንድን ነው? ብለህ ስትጠይቅ ለእኔ የሚሆነኝ ምላሽ በአጭሩ ምን መሰለህ ከሰብኣዊነት ፍጥረት ውጪ ሆነዋል ብዬ ለማመን እገደዳለሁ፨እኛ እዚሁ አፍንጫችን ሥር ያለውን ብቻ ዓይተን ነው የተገረምነው በዚህ ዓይነት በሃገሪቷ ላይ ስንት ንፁሃን ናቸው እየተሰቃዩ ያሉት፤ ቤት ንብረታቸው ፈርሶ፤ ከአብራካቸው የወጡ የት ይደርሳሉ የተባሉ ልጆቻቸውን አጥተው የግፍና የመከራ ፅዋቸውን ቀምሰው ለበሽታና ለሞት የተዳረጉትን ቤት ይቁጠራቸው፨ከስልክ ቤት እንደወጣች በጣም እንደተረበሸች በፊቷ ላይ ያስታውቃል፤ ቤት እንደገባች መሬት ላይ የተነጠፈው ፍራሽ ላይ ድፍት በማለት ስቅስቅ ብላ ማልቀስ ጀመረች፤ከዚያም ትንሽ ትንፋሿን መለስ ስታደርግ ትከሻዋን ዕቅፍ አድርጎ ምን ሰምተሽ ነው? እቤት ደህና አይደሉም እንዴ? አላት፨ የሰፈራችን ልጆች ምንም አልተረፉም፤ አልቀዋል በቃ! እነኚህ አረመኔዎች ከእስር ቤት በሌሊት እየወሰዱ ረሸኗቸው፤ ሰፈሩ ሁሉ ሀዘን በሃዘን ሆኗል፤ብለው ነግረውን ነው፤ የእኛ ቤተሰቦች እስከ አሁን ደህና ናቸው፨ከሁሉም ከሁሉም ያንገበገበኝ አንዱ ለእናቱ አንድ ነው፤ ሌላ ልጅ የላቸውም በስተእርጅና ተወለደ ልጅ ነው፤ ከዚህ በኋላ መውለድ አይችሉም ይሄንኑም በየቤቱ እየዞሩ እንጀራ እየጋገሩ ነው አሳድገው ያስተማሩት ያለ አባት፤ አባትዬው ወታደር ናቸው በሰሜኑ ግንባር ተሰውተው መርዶ ከተነገራቸው ስድስት ወር ቢሆናቸው ነው፤ልጁም እንዴት ያለ ጎበዝ መሰለህ እናቱን ያግዛቸዋል፤ በትምህርቱም ጎበዝ ነው፤ በዚህ ዓመት የአሥራ ሁለተኛ ብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ ነበር በአጭር አስቀሩት እንጂ፤ እናትዬው መርዶው ሲነገራቸው እንደ ዕብድ ነው የሆኑት አሉ፤እስከ አሁን ራሳቸውን አያውቁም ነው የሚባለው ከዚህ በኋላ ጤነኛም የሚሆኑ አይመስለኝም፤ ሊሆኑም አይችሉም ተስፋ የጣሉበትን ልጃቸውን፤ በችግርና በስቃይ በእሳት ተተብሰው፤ የሰው ፊት እየገረፋቸው እዚህ ያደረሱትን ልጃቸውን ሲነጠቁ ከዚህ በኋላ ምን ኑሮ አለኝ ብለው ይፅናናሉ፨ ኧረ እንዴት ያለ ጨካኝ የተፈጠረበት ዘመን ነው፨ ያ አላህ! ያ አላህ! ያ አላህ!ወጣቱ እንዲህ ደሙ ደመ ከልብ ይሁን? ለሃገሬ፤ ለጭቁኑ ወገኔ፤ ለዲሞክራሲ፤ ለፍትህና ለእኩልነት ብሎ የሚያደርገው ትግል መጨረሻው እንዲህ ይሁን፤ ያሳዝናል፤ .ወላጆችስ አሳድገው አስተምረው ለወግ ለማዕረግ ይበቁልኛል ብለው ሲጠብቁ ከነጭራሹ የልጆቻቸውን አስከሬን እንኳን ተከልክለው በወጉ ሳይቀብሩ፤ እንደልባቸው ጮኸው እርማቸውን ማውጣት ተከልክለው ውስጣቸው እንደበገነ እነሱም ለበሽታና ሞት ተዳርገው ይቅሩ የሚገረም ነው መሀመድ እኔ እስከ መቼም ከአዕምሮዬ የሚጠፋ አይደለም፤ አለች ዕንባዋ ዱብ ዱብ እያለ ፨በፓርቲያቸው የላዕላይ መዋቅር የተሰባሰቡት የትግል ጓደኞቻቸውም አብዛኛዎቹ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ትምህርታቸውን ጀምረው ያቋረጡ፤ ያጠናቀቁና ስለ ፓርቲያቸውና የሃገሪቷን ፖለቲካ ዕንቅስቃሴ እንዲሁም የዓለምን ተገንዝበው ለማስገንዘብ፤ ታግለው ለማታገል ብቃት ያላቸው ናቸው፨ይሁን እንጂ የፓርቲው የታችው ወይም የታህታይ መዋቅሩ አብዛኛው አባላት ግን ስለፓርቲያቸውና በፓርቲያቸው ውስጥ ስለሚካሄደው ፖለቲካዊ ጉዳይ ጠንቅቀው የማያውቁ በፓርቲው የዲሲፕሊን ህግ ተጨምድደው የተያዙ፤ ለምን ብለው የማይጠይቁና ቢጠይቁም እንደነውር የሚቆጠርባቸውና የዲሲፕሊን ህጉን እንደተላለፉ አድርገው የሚያስቡ ናቸው፨እነኚህ አባላት ግን ለሃገራቸው ሰላም፤ ዕድገት፤ ዲሞክራሲና ፍትህ፤ ለህዝቦች ዕኩልነት፤ ለጭቁኑ ህዝባቸው በደል በመቆርቆር፤ ለሚታገሉለት የህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ ጥልቅ ፍቅርና ታማኝነት ያላቸውና ወደ ትግሉ በመሰማራት ግንባራቸውን ለጥይት፤ አካላቸውን ለግርፋት፤ ለእስርና ለእንግልት በመስጠት ክቡር ህይወታቸውን ለቆሙለት ዓላማ ያስረከቡ የሃገሪቷ ህዝቦች የቁርጥ ቀን ልጆች ናቸው፨ሆኖም ግን ይህ ትግላቸው በወታደሮቹና ካድሬዎቻቸው በተጠነሰሰ ዕኩይ የቀይ ሽብር የጭካኔ ተግባር፤ በፓርቲው የላዕላይ መዋቅር በተፈጠረ የአንጃነት ሴራና ተንኮል፤ ሃገራቸውን ለማፈራረስና ህዝቡንም ለመበታተን በቆሙ የነፃነት ታጋዮች ነን በሚሉ ተገንጣዮች መሰሪ አካሄድ ፓርቲያቸው እንዲበተንና በሃገር ውስጥ የሚደረገው የትግል ዕንቅስቃሴም እንዲከሽፍ ተደርጓል፨ይህ በእንዲህ እያለ ፋሽስቱ ደርግ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲውን እንዳፈራረሰው፤ የላዕላይ መዋቅሩ ከፍተኛ አባላትም መመታታቸውንና መደምሰሳቸውን በመግለፅ የታህታይ መዋቅሩም አባላት በቁጥጥር ስር ውለው እርስ በእርሳቸው እየተገላለጡ ወደ አብዮቱ ካምፕ መግባታቸውን በየዕለቱ በሚያደርገው የፕሮፖጋንዳ ቅስቀሳ በሬዲዮን እየገለፀ ይገኛል፨ሆኖም ግን እስከ አሁን ድረስ በእስር ቤት የሚገኙትን ወጣቶች አለቀቃቸውም፤ የማሌ ጥናትና የአቋም ግምገማ በማለት በየአዳራሹ እየወሰደ ከፍተኛ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ በካድሬዎቻችው እየተደረገ ከዚያም ወደ ታሰሩበት እስር ቤት እንዲመለሱ ይደረግ ነበር፤ በዚህ ዓይነትም ለረጅም ወራት ከቆዩ በኋላ ደረጃ በደረጃ እየለቀቋቸው ወደ የቤተሰቦቻቸው እንዲቀላቀሉ አደረጓቸው፨ከእስር ከተፈቱት ውስጥ ጥቂት የማይባል ቁጥር ያላቸው ወጣቶች የአዕምሮ በሽተኛ ሆነዋል፤ የተወሰኑት ደግሞ በድብደባና በግርፋት ለአካለ ጎዶለነትና ለተለያዩ በሽታዎች ተጋልጠዋል፤ አንዳንድ ወንዶች በብልታቸው ላይ በደረሰባቸው ጉዳት ለመካንነት ሲዳረጉ፤ ሴቶች ወጣቶችም በአስገድዶ መደፈር ምክንያት የተጎዱና ሞራላቸው የወደቀ ሆነው፤ የማይፈልጉትን ፅንሰ ለማስወረድ የባህላዊ መድሃኒቶችን ለመጠቀም በወሰዱት እርምጃ ህይወታቸው ያለፈውን ቤት ይቁጠረው፤አብዛኛዎቹ የተፈቱት በህገ ወጥ መንገድ ወደ ባዕድ ሃገር እየተሰደዱ ሄዱ፤ በሃገሪቷ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ማለት ይቻላል በበዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ሃገራቸውን ጥለው ተሰደው የሄዱት በወታደሮቹ አገዛዝ ጊዜ ነው፨ በዚህ የተነሳም ሃገሪቷ በሺዎች የሚቆጠሩ የት ይደርሳሉ የተባሉ ከሞት የተረፉ የተማሩ ዜጎቿንና ተስፋ የተጣለባቸውን ወጣቶች ለባዕድ አገር ገብራለች፨ከዚያ ቀደም ብሎ የነበረን የተከበረ ስም ኢትዮጵያውያን ስደትን የሚጠየፉ፤ተምረው ሃገራቸውን ለማገልገል ጉጉት የነበራቸው፤ ለትምህርት ከሃገራቸው ሲወጡ እንኳን አጠናቀው የሚመለሱ እንጂ ዜግነታቸውን ቀይረው እዛው የሚቀሩ አልነበሩም ቢኖሩም በጣት የሚቆጠሩ ነበሩ፨ታዲያ በቀይ ሽብር ጦስ በተደረገው አሰቃቂ ግፍና መከራ የተነሳ ሳይወዱ በግድ ሃገራቸውን ጥለው እየሄዱ ለባዕድ ሃገራት አገልጋይ ቢሆኑና ጉልበታቸውንና ዕውቀታቸውን ሸጠው በመኖር ከነበሩበት የተሻለ አኗኗር ውስጥ ቢገቡም በሃገር ውስጥ በቀረው ወጣትና በቀጣዩ ትውልድ ላይ የፈጠረው የባዕድ ሃገር ናፋቂነት መጥፎ ባህልና የአመለካከት ችግር ፈጥሮ እንኳን ተምረውና ሰርተው ለሃገራቸው የተሻለ ነገር ለማምጣት የሚመኙ ሊሆኑ ይቅርና ይሄው እስከዛሬ ድረስ በሃገራቸው በነፃነት ሰርተው የመለወጥ ተስፋቸው የተሟጠጠ አድርገው እንዲያስቡና በስደት እየተንገላቱ እንዲኖሩ በር የከፈተው የወታደሮቹ አገዛዝ ነው፨ በቀጣይ የተተኩትም መንግስታት ይሄንን በማስተካከል ፋንታ እየተባባሰ እንዲመጣ አድርገውታል፨ Read more

ASIN B0DDCHBTDR
Language Afrikaans
File size 2.1 MB
Page Flip Enabled
Word Wise Not Enabled
Print length 143 pages
Accessibility Learn more
Publication date August 15, 2024
Enhanced typesetting Enabled

Correction of product information

If you notice any omissions or errors in the product information on this page, please use the correction request form below.

Correction Request Form

Customer ratings & reviews

4.5 out of 5
★★★★★
34 ratings | 14 reviews
How item rating is calculated
View all reviews
5 stars
83% (28)
4 stars
4% (1)
3 stars
2% (1)
2 stars
1% (0)
1 star
10% (3)
Sort by

There are currently no written reviews for this product.